ይህ ኮርስ በባህረ-ሰላጤው (Gulf) አገራት በመሄድ በቤት ውስጥ ስራ ለመሰማራት ለሚዘጋጁ ኢትዮጵያውያን ሴቶች የተዘጋጀ፣ የሙያ እና የባህል ድልድይ የሚሆን አጠቃላይ ስልጠና ነው።
ብዙ ሰራተኞች ወደ ባህረ-ሰላጤው አገራት ሲገቡ በሚገጥማቸው የቋንቋ እጥረት እና ጥብቅ የባህል ህጎች የተነሳ ለከፍተኛ ጭንቀትና አለመረጋጋት ይዳረጋሉ። ይህ ኮርስ በባህረ-ሰላጤው የአረብኛ Khaleeji የተሰኘ የአነጋገር ዘይቤ ፣በቤት አያያዝ እና የባህል እሴቶች ላይ ጥልቅ የሆነ ስልጠና በመስጠት፤ አንዲት ሰራተኛ የነበራትን ፍርሃት አስወግዳ በራሷ የምትተማመን ብቁ ባለሙያ እንድትሆን ያደርጋታል።
ሰልጣኞች ይህንን ስልጠና ሲያጠናቅቁ መሠረታዊ ትዕዛዞችን ለመረዳት ከመቸገር ተላቀው፤ ፍላጎታቸውን በግልጽ መግባባት የሚችሉ፣ ስራቸውን በብቃት የሚወጡ እና በስራቸው ተፈላጊና የተከበሩ ባለሙያ በመሆን ሙሉ የለውጥ ጉዞ ያደርጋሉ።